በሮም ማራቶን ለሻምበል አበበ ቢቂላ የመታሰቢያ መርሐ-ግብር ተካሄደ

360

አዲስ አበባ መጋቢት 10 2015(ኢዜአ):- በሮም ማራቶን ለሻምበል አትሌት አበበ ቢቂላ የመታሰቢያ ዝግጅት ተከናውኗል።

2023 ሮም ማራቶን ዛሬ በጣሊያን ሮም ከተማ ተካሄዷል።

የተዘጋጀው መርሐ-ግብር .. 1960 በሮም በተካሄደው 18ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች ሻምበል አትሌት አበበ ቢቂላ በማራቶን በባዶ እግሩ በመሮጥ ለኢትዮጵያ ያስገኘውን የወርቅ ሜዳሊያ ለመዘከር በማሰብ መሆኑም ተጠቅሷል።


 

በዚህም አትሌቱን ለማሰብ የድንቅ ኢትዮጵያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ኤርሚያስ አየለ የሻምበል አትሌት አበበ ቢቂላ ከዛሬ 63 ዓመት በፊት በሮም በተካሄደው የኦሊምፒክ ውድድር ማራቶን ላይ በባዶ እግሩ የሮጠውን በማሰብ የሮም ማራቶንን በባዶ እግር በመሮጥ የብዙዎችን ትኩረት ስበዋል።


 

በመርሃ-ግብሩ ላይ በጣሊያን የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ደሚቱ ሐምቢሳና በሮም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰራተኞች፣ በሮም የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የአትሌቱ ፎቶ ያረፈባቸውን ቲሸርቶች ለብሰው በመሮጥ አትሌቱን አስበውታል።


 

አምባሳደር ደምቱ በዝግጅቱ ለተሳተፉ ምስጋና ማቅረባቸውን በሮም የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያሳያል።

2023 የሮም ማራቶን በወንዶች ሞሮኳዊው አትሌት ታውፊክ አላም በሴቶች ኬንያዊቷ አትሌት ቤቲ ቼፕክዎኒ አሸንፈዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም