የሲዳማ ሴቶች በሀዋሳ ሰልፍ እያካሄዱ ነው - ኢዜአ አማርኛ
የሲዳማ ሴቶች በሀዋሳ ሰልፍ እያካሄዱ ነው
ሀዋሳ ሚያዝያ 1/2011 የሲዳማ የክልልነት ጥያቄን የተመለከተ በብሄሩ ተወላጅ ሴቶች የተጠራ ሰልፍ ዛሬ በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ነው ።
ማለዳ 12 ሰዓት በጀመረው ሰልፍ ከሁሉም የሲዳማ ዞን ወረዳዎችና ከተሞች የተወጣጡ ወጣት ሴቶችና እናቶች ተሳትፈውበታል ።
ከወልደአማኑኤል ዱባለ አደባባይ የተነሳው ሰልፉ መድረሻውን መስቀል አደባባይ ያደረገ ነው ።
ሰልፈኞቹ የሕዝብ ውሳኔ ቀን ተቆርጦ ይነገረን፣ጥያቄያችን ሕገ-መንግስታዊ ትግላችንም ሰላማዊ ነው፣ ጥያቄያችን በሕገ-በመንግስቱ መሰረት ብቻ ይመለስ፣ ፍትህ ለሲዳማ ሕዝብ የሚሉ መልእክቶችን አስተላልፈዋል ።