የአውሮፓ ህብረት ቦይንግ 737 ማክስ ስምንት አውሮፕላን በአውሮፓ አየር ክልል እንዳይበር አገደ - ኢዜአ አማርኛ
የአውሮፓ ህብረት ቦይንግ 737 ማክስ ስምንት አውሮፕላን በአውሮፓ አየር ክልል እንዳይበር አገደ
58
መጋቢት 3 / 2011 የአውሮፓ ህብረት ቦይንግ 737 ማክስ ስምንት አውሮፕላን በአውሮፓ አየር ክልል እንዳይበር ማገዱን ይፋ አደረገ፡፡
ቦይንግ 737 ማክስ ስምንት አውሮፕላን በአውሮፓ አየር ክልል እንዳይበር የታገደው ለ157 ሰዎች ህልፈት ምክንያት የሆነው በኢትዮጵያ በተከሰከሰው አውሮፕላን መነሻ በማድረግ ነው፡፡
የአውሮፓ አቬየሽን ደህንነት ኤጄንሲ (EASA) በመግለጫው እንዳስታወቀው በአውሮፓ የሚገኙ ሁሉም ቦይንግ 737 ማክስ ስምንት አውሮፕላን አገልግሎት መስጠት እንዲያቆሙ ተደርጓል፡፡
በሌሎች በሶስተኛ ወገን በንግድ የሚንቀሳቀሰሱ ቦይንግ 737 ማክስ ስምንት አውሮፕላኖች በአየር ክልሉ ውስጥ በረራ እንዳይደረግም አግዷል፡፡
የተከሰተውን አደጋ የማጣራት ሥራ እየተካሄደ ነው ያለው ህብረቱ፤ የአደጋውን መንስኤ ለማወቅም ግዜው ገና ነው ብሏል፡፡
በተመሳሳይ መልኩ የኢንግሊዝ ሲቪል አቬየሽን ባለስልጣን፣ ቻይና ፣ ስንጋፖርና አውስትራሊያን የመሳሰሉት ሀገራት ቦይንግ 737 ማክስ
ስምንት አውሮፕላን በአየር ክልላቸው እንዳይበር ማገዳቸው ይታወሳል ሲል የዘ ኢንዲፐንዴንት ዘገባ ያመለክታል፡፡