ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ

274

አዲስ አበባ (ኢዜአ) የካቲት 1/2015 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡

May be an image of one or more people and indoor

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር መወያየታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ላለፉት ሁለት ቀናት በአውሮፓ ጣሊያን፣ ማልታና ፈረንሳይ ስኬታማ ጉብኝት አድርገው ዛሬ ማለዳ ወደ አዲስ አበባ መመለሳቸው ይታወቃል።

በጉብኝታቸውም ከሀገራቱ መሪዎች ጋር በሁለትዮሽና ዓለም አቀፋዊ የትብብር መስኮች የጋራ መግባባት ላይ መድረሳቸው የሚታወቅ ነው።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም