በሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ - ኢዜአ አማርኛ
በሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ
![](/documents/42135/0/2023_01_323128819_6040334652760566_4183134871543667976_n_jpg.jpg/ebee5fb6-7ef1-ace2-2b85-75467e4d1fb5?version=1.0&t=1675489365592&download=true)
አዲስ አበባ (ኢዜአ) ጥር 7/2015 ዛሬ ማለዳ በሕንድ በተካሄደው የሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ።
![](https://www.ena.et/wp-content/uploads/2023/01/322510131_591156066169323_7184038837849193606_n.jpg)
በሴቶች ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 8ኛ ተከታትለው በመግባት የበላይነቱን ይዘዋል።
![](https://scontent.fadd2-1.fna.fbcdn.net/v/t39.30808-6/325791366_698193445106290_5536471269730076550_n.png?stp=dst-png_p526x395&_nc_cat=104&ccb=1-7&_nc_sid=730e14&_nc_ohc=rGtyg9KkTDcAX_n8oWI&_nc_ht=scontent.fadd2-1.fna&oh=00_AfCvcoh1mEgX1ULPgNKVa1IeZFtAovQH6fwNsgMSmCm8XQ&oe=63C97CE3)
በውድድሩ አትሌት አንቺዓለም ሃይማኖት 2 ሰአት ከ24 ደቂቃ ከ15 ሴኮንድ በመግባት አሸናፊ ስትሆን የቦታውንም ክብረወሰን አሻሽላለች።
አትሌት ረሂማ ቱሳ እና አትሌት ለተብርሃን ኃይላይ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ወጥተዋል።
![](https://scontent.fadd2-1.fna.fbcdn.net/v/t39.30808-6/325796613_547063917353427_1982932256951298594_n.png?stp=dst-png_p600x600&_nc_cat=105&ccb=1-7&_nc_sid=730e14&_nc_ohc=uhLHBpnYfu8AX9e4OcO&_nc_ht=scontent.fadd2-1.fna&oh=00_AfAuRcTanjIwTFp1GPEygKW3uBmO8KqI4kaL4K85D1EhbQ&oe=63C93DBE)
በወንዶች አትሌት ለሚ ብርሃኑ 2 ሰአት ከ7 ደቂቃ ከ32 ሴኮንድ በመግባት አሸንፏል። የቦታውንም ክብረ ወሰን ማሻሻል ችሏል።
ኬንያዊው አትሌት ፊልሞን ሮኖ ሁለተኛ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ኃይሉ ዘውዱ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል።