በሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ - ኢዜአ አማርኛ
በሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ

አዲስ አበባ (ኢዜአ) ጥር 7/2015 ዛሬ ማለዳ በሕንድ በተካሄደው የሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ።

በሴቶች ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 8ኛ ተከታትለው በመግባት የበላይነቱን ይዘዋል።

በውድድሩ አትሌት አንቺዓለም ሃይማኖት 2 ሰአት ከ24 ደቂቃ ከ15 ሴኮንድ በመግባት አሸናፊ ስትሆን የቦታውንም ክብረወሰን አሻሽላለች።
አትሌት ረሂማ ቱሳ እና አትሌት ለተብርሃን ኃይላይ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ወጥተዋል።

በወንዶች አትሌት ለሚ ብርሃኑ 2 ሰአት ከ7 ደቂቃ ከ32 ሴኮንድ በመግባት አሸንፏል። የቦታውንም ክብረ ወሰን ማሻሻል ችሏል።
ኬንያዊው አትሌት ፊልሞን ሮኖ ሁለተኛ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ኃይሉ ዘውዱ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ ጨርሷል።