በአማራ ክልል" የሌማት ትሩፋት" ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር እየተካሄደ ነው

220

ቻግኒ ኢዜአ ህዳር 18 ቀን 2015 በአማራ ክልል "የሌማት ትሩፋት" ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር በቻግኒ ከተማ ይፋ እየተደረገ ነው።

በመርሃ-ግብሩ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ይልቃል ከፋል፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎና ሌሎች የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

May be an image of 4 people, people sitting, people standing and indoor

የሌማት ትሩፋት ተመጣጣኝ ምግብ በብዛት እና በጥራት በገበያው እንዲኖር በማድረግ ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ የምግብ ስርዓት መዘርጋትን አላማ ያደረገ እንደሆነ ተመላክቷል።

የሌማት ትሩፋት የክልሉን የእንስሳት ሃብት ምርታማነት በማሳደግ የሁሉንም ዜጎች የአመጋገብ ስርዓት ለማሻሻል የሚያግዝ ነውም ተብሏል።

በተለይም ስጋ፣ እንቁላል፣ማር እና ወተት የቅንጦት ምግቦች ሳይሆኑ አቅርቦቱን በማስፋት ጤንነቱ የተጠበቀ ማህበረሰብ ለመገንባት ጭምር ታሳቢ በማድረግ የጀመረ ፕሮግራም ነው።

May be an image of food and indoor

የሌማት ትሩፋት በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ መሪነት በዚህ ወር ይፋ መደረጉ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም