ዩኒቨርሲቲው በየኮሌጆቹ የተሻለ የምርምር ስራ ለሰሩ ተመራማሪዎች፣ ተማሪዎችና አሳታሚዎች እውቅና ሰጠ - ኢዜአ አማርኛ
ዩኒቨርሲቲው በየኮሌጆቹ የተሻለ የምርምር ስራ ለሰሩ ተመራማሪዎች፣ ተማሪዎችና አሳታሚዎች እውቅና ሰጠ
![](/documents/42135/0/2022_11_316107403_508143631339347_9089367229944193314_n_jpg.jpg/1dedf09a-fdd7-c08e-2830-778a26658056?version=1.0&t=1674400611425&download=true)
አዲስ አበባ (ኢዜአ) ህዳር 12 ቀን 2015 አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በየኮሌጆቹ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ተመራማሪዎች፣ ተማሪዎችና አሳታሚዎች እውቅና ሰጥቷል።
በስድስት ኪሎ ካምፓስ በተዘጋጀው መርሃ-ግብር ላይ የዓመቱ ምርጥ ተመራማሪ መምህራንና ተማሪዎች እንዲሁም አሳታሚዎች እውቅና ተሰጥቷል።
በእውቅና መርሀ-ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ፕሬዝደንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሀና በተለያዩ የትምህርት መስኮች የምርምር ስራዎችን ያበረከቱ ምሁራን ተገኝተዋል።
በቅርቡ ከዩኒቨርሲቲው የፕሮፌሰርነት ማዕረግ የሰጣቸው ተመራማሪዎች ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
![](https://www.ena.et/wp-content/uploads/2022/11/photo_2022-11-21_15-07-22.jpg)
ሽልማቱ የተሰጣቸው ምሁራን የምርምር ስራዎቻቸው አግባብ ባላቸው ጆርናሎች ያሳተሙ የአገልግሎት ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ እና በማህበረሰብ ግልጋሎት የሚጠበቅባቸውን አስተዋጽኦ ያበረከቱ መሆናቸውም ተገልጿል።
ዩንቨርሲቲው ባለፉት ስድስት ወራት ብቻ ከ 2 ሺህ 800 በላይ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆኑ የምርምር ስራዎች ለህትመት እንዳበቃ በመርሀ-ግብሩ ላይ ተገልጿል።
በምርምር ስራዎቹ ላይ አስተዋጽኦ ላበረከቱ መምህራን፣ ተማሪዎች እና አመራሮች እውቅና ተሰጥቷል።
የዩንቨርሲቲው ፕሬዝደንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሀና በኢኮኖሚክስ ዘርፍ ባለፉት ስድስት ወራት 14 የምርምር ጽሁፎችን በማሳተም እውቅና ተበርክቶላቸዋል።