ቀጥታ፡

የክቡር ዶክተር አሊ ቢራ ስርዓተ ቀብር በድሬዳዋ ለገሀሬ እስላም መቃብር ተፈጸመ

ድሬዳዋ (ኢዜአ) ጥቅምት 29/2015 የክቡር ዶክተር አርቲስት አሊ ቢራ ስርዓተ ቀብር በድሬዳዋ ለገሀሬ እስላም መቃብር ተፈጸመ ።

የአርቲስት አሊ ቢራ አስክሬን የሽኝት እና የጸሎት ፕሮግራም በድሬዳዋ ከተማ እስታዲየም የተካሄደ ሲሆን የቀብር ስነስርዓቱ ላይ ወዳጅ ዘመድ፣ሙያ አጋሮቹ፣ ከፍተኛ የመንግሥት ስራ ኃላፊዎች ፣በርካታ የድሬዳዋ እና አካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል ።

ክብር ዶክተር አርቲስት ዓሊ ቢራ በአዳማ አጠቃላይ ሆስፒታል በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በ75 ዓመቱ ከትናንት በስቲያ ሕይወቱ ማለፉ ይታወቃል።

አርቲስቱ ስለአንድነት ፣አብሮነት ፣ፍቅር ፣ሰላምና ፍትህን ጨምሮ በበርካታ ስራዎች ላይ አቀንቅኗል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም