ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት የካውንስል አባል ሆና ተመረጠች

መስከረም 25 /2015 (ኢዜአ) ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት የካውንስል አባል ሆና መመረጧን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ ገለጹ።

ኢትዮጵያ በካናዳ ሞንትሪያል በመካሄድ ላይ በሚገኘዉ 41ኛዉ የዓለም አቀፍ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት በከፍተኛ ድምጽ የካውንስል አባል ሆና መመረጧን ሚኒስትሯ በማኀበራዊ የትስስር ገፃቸው ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም