አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው በለንደን ማራቶን አሸነፈች - ኢዜአ አማርኛ
አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው በለንደን ማራቶን አሸነፈች

መስከረም 22 ቀን 2015 (ኢዜአ) አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው ዛሬ የተካሄደውን የለንደን ማራቶን ውድድር አሸነፋች፡፡
ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው በለንደን ማራቶን 2:17:26 በሆነ ሰዓት በአንደኝነት ጨርሳለች።
ኬንያዊቷ አትሌት ጆይሲሊን ጄፕኮስጌይ በውድድሩ 2:18:07 በሆነ ሰዓት 2ኛ ስትወጣ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት መገርቱ ዓለሙ ደግሞ 2:18:32 በሆነ ሰዓት 3ኛ ወጥታለች።
በተመሳሳይ በለንደን በተካሄደ የወንዶች የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ልዑል ገብረሥላሴ በ 2:05:12 በሆነ ሰዓት 2ኛ ወጥቷል።

ውድድሩን ኬንያዊው አትሌት አሞስ ኪፕሩቶ 2:04:39 በሆነ ሰዓት 1ኛ በመውጣት አሸንፏል።
ሌሎች ኢትዮጵያውያን አትሌት ክንዴ አጣናው 4ኛ፣ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ 5ኛ፣ አትሌት ብርሃኑ ለገሰ 6ኛ እና አትሌት ሲሳይ ለማ 7ኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቅቀዋል፡፡