በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የኦሞ እና የከፋ ዞኖች ለሰራዊቱ ከ38 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ አደረጉ - ኢዜአ አማርኛ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የኦሞ እና የከፋ ዞኖች ለሰራዊቱ ከ38 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ድጋፍ አደረጉ

መስከረም 13/2015 (ኢዜአ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የኦሞ እና ከፋ ዞኖች ለሀገር መከላከያ ሰራዊቱ ከ38 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የገንዘብና የአይነት ድጋፍ አደረጉ፡፡
የከፋ ዞን ከ31 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብና የአይነት ድጋፍ ያደረገ ሲሆን፤ድጋፋን የዞኑ የመንግስት ተጠሪ አቶ አስረስ አስፋው ለመከላከያ ሚኒስትር ዴኤታ ማርታ ሊውጂ አሰረክበዋል።
የምዕራብ ኦሞ ዞን ደግሞ ከ 6 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የአይነትና የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
በቀጣይም ድጋፉን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ነው የገለጹት፡፡