1443 ኛው የኢድ አል አድሀ( አረፋ ) በዓል እየተከበረ ነው - ኢዜአ አማርኛ
1443 ኛው የኢድ አል አድሀ( አረፋ ) በዓል እየተከበረ ነው
ሐምሌ 2 ቀን 2014(ኢዜአ) 1443ኛው የኢድ አል አድሀ( አረፋ ) በዓል እየተከበረ ይገኛል::
በአዲስ አበባ እየተከበረ ባለው በዓል የሶላት ስነ ስርአት ላይ የሚታደሙ የእምነቱ ተከታዮች ትንሿ ስታዲየም እየገቡ ነው::
በአሁኑ ወቅት በስታዲየሙ ምስጋና የሚቀርብበት ተክቢራ እየተደረገ ሲሆን ተክቢራው እንደተጠናቀቀም የሶላት ስነ ስርዓት የሚካሄድ ይሆናል::
አማኞች ከሶላት በሁዋላ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ እርድ በማካሄድ እና ለሌላቸው በማካፈል በዓሉን ያሳልፋሉ::
1443ኛው የኢድ አል አድሀ( አረፋ ) በዓል በመላው አለም በእስልምና ተከታዮች ዘንድ ዛሬ ተከብሮ ይውላል::
ኢትዮጵያን እናልማ፣እንገንባ፣እንዘጋጅ