በኢትዮጵያ በአራት አመታት ውስጥ 20 ቢሊዮን ችግኞችን የመትከል እቅድ ዘንድሮ ይሳካል -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

105

ሰኔ 12 ቀን 2014 (ኢዜአ)በኢትዮጵያ በአራት አመታት ውስጥ 20 ቢሊዮን ችግኞችን የመትከል እቅድ ዘንድሮ እንደሚሳካ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንደገለጹት በዘንድሮው ክረምት በአረንጓዴ አሻራው 6 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል ዝግጅት ተደርጓል።

May be an image of 5 people, child, people standing, tree and outdoors

የአረንጓዴ አሻራውም ሰኔ 14 ቀን እንደሚጀመር የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለመርሃ ግብሩም 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን ችግኞች ተዘጋጅተዋል ነው ያሉት።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም