ኢትዮጵያና ጣሊያን የ22 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ

102

ሰኔ6/2014/ኢዜአ/ ኢትዮጵያና ጣሊያን የ22 ሚሊዮን ዩሮ የብድር ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

ስምምነቱን በገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴና የጣሊያን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሉዋጂ ዲ ማዩ ተፈራርመዋል።

ገንዘቡም ቡልቡላ፣ ቡሬ፣ይርጋለምና ባዕከር ለሚገኙ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ማጠናከሪያ እንዲሁም በፓርኮቹ ዙሪያ ለሚቋቋሙ የገጠር ሽግግር ማዕከላት ግንባታ የሚውል ነው።

May be an image of 7 people and people standing

የብድር ስምምነቱን የጣሊያን እና ኢትዮጵያ ያላቸውን ኢኮኖሚ ትብብር የሚያጠናክር መሆኑንም ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ገልፀዋል።

የጣሊያን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሉዋጂ ዲ ማዩ በበኩላቸው ስምምነቱ ጣሊያን ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት እንደሚያሳይ  አብራርተዋል፡፡

የብድር ስምምነቱ  በኢትዮጵያ እየተተገበረ ለሚገኘው የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስኬታማነት እንደሚያግዝም ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም