ወደ ትግራይ ክልል የሰብዓዊ እርዳታ ጭነው የተጓዙ 50 ከባድ ተሽከርካሪዎች መቀሌ ገቡ

666

ሚያዚያ 07 ቀን 2014 (ኢዜአ) ሰሞኑን ወደ ትግራይ ክልል የሰብዓዊ እርዳታ ጭነው የተጓዙ 50 ከባድ ተሽከርካሪዎች በሰላም መቀሌ መግባታቸውን የዓለም የምግብ ፕሮግራም አስታወቀ።

የዓለም ምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ቢሮ በትዊተር ገጹ እንዳስነበበው፤ ተሽከርካሪዎቹ ወሳኝ የሰብዓዊ ድጋፍ ጭነዋል።

ከጫኑት ውስጥ ስንዴ፣ የቅባት እህልና ነዳጅ እንደሚገኝበት ጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም