ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎ የደቡብ ክልል ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ ሆኑ - ኢዜአ አማርኛ
ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎ የደቡብ ክልል ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ ሆኑ
መስከረም 22/2014 የመንግስት ምስረታ ጉባኤ እያካሄደ ያለው የደቡብ ክልል ምክር ቤት ወይዘሮ ፋጤ ስርሞሎን የምክር ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ አድርጎ መርጧል ።
አፌ ጉባኤውን ያቀረቡት የደቡብ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ጥላሁን ከበደ ናቸው ።
አቶ ጥላሁን 6ኛው ምርጫ ያልተመለሱ ጥያቄዎች በአግባቡ መመለስ ይችላል ብለው በህዝብ በመመረጥ ቦታ ብንይዝም አሸናፊው ህዝቡ ነው ብለዋል ።
ቀጣይ በሚኖረው ጊዜ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ለህዝባችን ተጠቃሚነት እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል ።
ወይዜሮ ፋጤ ስርሞሎ ከወረዳ ጀምሮ በክልሉ በተለያዩ የስራ ሀላፊነት በብቃት ማገልገላቸው ተገልጿል ።
ወይዘሮ ፋጤ በክልሉ ብልጽግና የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ ሆነው ሰርተዋል።
ተሿሚዋ የተጣለባቸውን ሃላፊነት ለመወጣት በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሃላ ፈጽመዋል