ቀጥታ፡

አቶ ርስቱ ይርዳው የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ተመረጡ

መስከረም 22/2014 (ኢዜአ) አቶ ርስቱ ይርዳው የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው ተመረጡ ።

አቶ ርስቱ ለበርካታ ዓመታት ከወረዳ እስከ ፌዴራል ድረስ በተለያዩ የሥራ መስኮች ተሰማርተው ውጤታማ አፈጻጸም የነበራቸው መሆኑን ገልጸዋል ።

ስነምግባር ተነሳሽነት ታማኝነትና ትጋት እንዲሁም የአመራር ብቃት እንዲመረጡ ያደረጋቸው መሆኑን ገልጸዋል ።

በተለይም ባለፉት የለውጥ ዓመታት ያጋጠሙ ችግሮችን በበሳል አመራር በማሻገር አሁን ላለው ልማት ማድረሳቸውን ገልጸዋል። 

የምክር ቤቱ አባላት በቀረቡት ዕጩ አስተያየት በመስጠት በሙሉ ድምጽ አጽድቋል ።

አቶ ርስቱ ይርዳው የተጣለባቸውን ሀላፊነት በታማኝነት ለመወጣት በምክር ቤት ፊት ቀርበው ቃለ መሀላ ፈጽመዋል ።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም