ዶክተር ሊያ ታደሰ ከአዲሱ የዩኒሴፍ የኢትዮጵያ ተወካይ ጋር ተወያዩ - ኢዜአ አማርኛ
ዶክተር ሊያ ታደሰ ከአዲሱ የዩኒሴፍ የኢትዮጵያ ተወካይ ጋር ተወያዩ
245
አዲስ አበባ (ኢዜአ) ጥር 29/2015 የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ከአዲሱ የዓለም አቀፉ የህጻናት አድን ድርጅት (ዩኒሴፍ) የኢትዮጵያ ተወካይ አቡባካር ካምፖ ጋር ተወያዩ።
ሚኒስትሯ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሳፈሩት መልዕክት ተቋማቱ በትብብር በሚያከናውኗቸው የህጻናት ጤና፣ስርዓተ-ምግብ እና የአስቸኳይ ግዜ ምላሽን በተመለከተ ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
በተጨማሪም ዩኒሴፍ ለሚያደርገው ድጋፍ አድናቆታቸውን ገልጸው፤ በቀጣይ ከድርጅቱ ጋር ያለውን አጋርነት ለማጠናከር ሚኒስቴሩ ያለውን ቁርጠኝነት አስታውቀዋል።