የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሺመልስ አብዲሳ በምሥራቅ ወለጋ ዞን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተወያዩ

ጥር 8/2015 (ኢዜአ) የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሺመልስ አብዲሳ በምሥራቅ ወለጋ ዞን ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ገለጸ።

May be an image of one or more people and people standing

በውይይት ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ ወታደራዊ መኮንኖች፣ አባ ገዳዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።

በተከሰተው የፀጥታ ችግር የሰዎች መፈናቀል፣ የንብረት ዘረፋ እና የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ችግሮች ማጋጠሙን የውይይቱ ተሳታፊዎች አንስተዋል።

May be an image of 2 people, people standing, military uniform and outdoors

መንግስት የፀጥታ ችግሮችን በመፍታት የመሠረተ ልማት ችግሮችንና ሥራ አጥነትን ለመፍታት በትኩረት እንዲሰራ ተሳታፊዎቹ መጠየቃቸው ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም