ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አምባሳደር ምስጋኑ አረጋን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አድርገው ሾሙ - ኢዜአ አማርኛ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አምባሳደር ምስጋኑ አረጋን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አድርገው ሾሙ

አዲስ አበባ (ኢዜአ) ጥር 3 /2015 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አምባሳደር ምስጋኑ አረጋን ከጥር 02 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አድርገው ሹመዋል።
አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው እስከ ተሾሙበት ጊዜ ድረስ የኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተዋል።
አምባሳደር ምስጋኑ ቀደም ሲል በኳታር እና በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው ማገልገላቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል-አቀባይ ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።