ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በፕሮጀክቶች ስራ ላይ እየተሳተፉ ለሚገኙ ሠራተኞች ማዕድ አጋሩ

አዲስ አበባ (ኢዜአ) ታህሳስ 30/2015 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጽሕፈት ቤታቸው በሚመሩ የልማት ፕሮጀክቶች እየተሳተፉ ለሚገኙ ሠራተኞች ማዕድ አጋርተዋል።

May be an image of one or more people and indoor

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የሚመሩ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ላይ እየተሳተፉ ለሚገኙ ሠራተኞች ነው የበዓል ማዕድ ያጋሩት።

May be an image of 1 person and indoor

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትላንትናው እለትም በዓልን ምክንያት በማድረግ ከአዲስ አበባ ሁሉም ከፍለ ከተሞች ለተውጣጡ በድምሩ 150 ለሚሆኑ አረጋዊያን፣ አካል ጉዳተኞችና የጎዳና ተዳዳሪዎች የበዓል ማዕድ ማጋራታቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

May be an image of 8 people, people standing and indoor
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም