የቻይና ኤምባሲ የአዲስ አበባ ከተማን የአገልግሎት አሰጣጥ የሚያሻሽሉ የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶች አበረከተ - ኢዜአ አማርኛ
የቻይና ኤምባሲ የአዲስ አበባ ከተማን የአገልግሎት አሰጣጥ የሚያሻሽሉ የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶች አበረከተ
114
አዲስ አበባ /ኢዜአ/ ህዳር 12/2015 /የቻይና ኤምባሲ የአዲስ አበባ ከተማን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻል የሚረዱ የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ ።
የቻይና ኤምባሲ የከተማ አስተዳደሩን የአገልግሎት አሰጣጥ የሚያሻሽሉ ድጋፎች ማድረጉ የአገልግሎት አሰጣጡን እንደሚያቀላጥፈው የከተማዋ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻችው አስፍረዋል ።
በዚህም “የከተማ አስተዳደራችን የአገልግሎት አሰጣጡን ይበልጥ ለማሻሻል በሚያደርገው ጥረት የቻይና ኤምባሲ አሰራሩን የሚያጠናክሩ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ እና የአገልግሎት ቁሳቁሶችን ድጋፍ ስላደረገልን እናመሰግናለን” ብለዋል።