"የነገዋ ኢትዮጵያ የተሻለች እንድትሆን የተሻለ ትውልድ እያፈራን እንቀጥላለን"-ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ

137

ጥቅምት 20/2015 (ኢዜአ) "የነገዋ ኢትዮጵያ የተሻለች እንድትሆን የተሻለ ትውልድ እያፈራን እንቀጥላለን" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ገለጹ።

የወዳጅነት ፓርክ ሁለተኛው ምዕራፍ ዛሬ ለአገልግሎት ክፍት መደረጉን አብስረዋል።

May be an image of 10 people and outdoors

ፓርኩ ስፖርትን፣ ጨዋታንና ማኅበራዊ መስተጋብርን ያቀናጀ መሆኑን አስረድተዋል። ልጆች እየተጫወቱ ሳይንስና ቴክኖሎጂን ይለማመዳሉ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፓርኩ ወጣቶች ያነብባሉ፣ ስፖርትም ይሰሩበታል ነው ያሉት።

May be an image of 9 people, child, people standing, footwear and outdoors

ወላጆችና አያቶች ከልጆቻቸው ጋር መጥተው ማኅበራዊ ልምዳቸውን ይለዋወጡበታል ብለዋል።

አዲስ ተጋቢዎች በሠርግ ዐጸዱ ጋብቻቸውን ይመሠርታሉ ሲሉም ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የነገዋ ኢትዮጵያ የተሻለች እንድትሆን የተሻለ ትውልድ እያፈራን እንቀጥላለን ሲሉ ነው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ያስታወቁት ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ቁጥር ሁለት ወዳጅነት አደባባይን ዛሬ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት ማድረጋቸው ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም