ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካቸው በፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ከሚመራው የኬንያ ሪፐብሊክ ልዑካን ጋር ተወያዩ

143

አዲስ አበባ መስከረም 26/ 2015 (ኢዜአ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ልዑካቸው በፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ ከሚመራው የኬንያ ሪፐብሊክ ልዑካን ቡድን ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አድርገዋል።

May be an image of 2 people, people sitting, people standing and indoor

በኢትዮጵያ እና በኬንያ መካከል ያለውን ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ሁለቱ መሪዎች መናገራቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መረጃ አመልክቷል።

ኢትዮጵያ እና ኬኒያ ጋር ለረዥም ጊዜ የዘለቀ ወዳጅነት እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሰረት ትብብር ያላቸው አገራት ናቸው።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም