ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሶማሊያ ፕሬዚዳንትን ተሰናበቱ - ኢዜአ አማርኛ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሶማሊያ ፕሬዚዳንትን ተሰናበቱ
143
መስከረም 20 / 2015 (ኢዜአ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድን ተሰናበቱ።
ፕሬዚዳንቱ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ሲያደርጉ መቆየታቸው ይታወቃል።
በጉብኝቱም ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ እና የሶማሊያ አቻቸው ሀሰን ሼህ ሞሀመድ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት ያደረጉ ሲሆን በተለይ በቀጠናው ሽብርተኝነትንና አክራሪነት በትብብር መዋጋት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ እንዲሁም በሁለትዮሽ የኢኮኖሚ ትብብር ላይ መወያየታቸው በወጣው የጋራ የአቋም መግለጫ ማወቅ ተችሏል።