የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ)አመራሩን መረጠ - ኢዜአ አማርኛ
የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ)አመራሩን መረጠ
144
ጅማ መስከረም 11/2011 የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኦዴፓ) 55 የማዕከላዊ ኮሚቴና ሥራ አስፈጻሚ አባላትን መረጠ። ኦዴፓ በጅማ እያደረገ ባለው ድርጅታዊ ጉባዔው 55 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን የመረጠ ሲሆን፤ ለኢህአዴግ ምክር ቤት አባልነትም 45 አባላትን መርጧል። በማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ለመመረጥ የተጠቆሙት 60 እጩዎች ናቸው። ጉባኤው በሰጠው ድምጽ መሰረትም ዶክተር አብይ አህመድን የድርጅቱ ሊቀመንበር፣ አቶ ለማ መገርሳን ደግሞ በምክትል ሊቀመንበርነት መርጧል። የፓርቲው ሊቀመንበር ዶክተር አብይ አህመድና ምክትል ሊቀመንበር አቶ ለማ መገርሳን ጨምሮ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ፣ አቶ አዲሱ አረጋ፣አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣አቶ ብርሃኑ ጸጋዬ፣ አቶ ፍቃዱ ተሰማ፣ ወ/ሮ አዳነች አበቤ እና ዶክተር ዓለሙ ስሜ በስራ አስፈጻሚነት ተመርጠዋል። የማዕከላዊ ኮሚቴ ሆነው ከተመረጡት አባላት መካከልም ለኢህአዴግ ምክር ቤት አባልነት የተመረጡት፡-
- ዶክተር አብይ አህመድ
- አቶ ለማ መገርሳ
- ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ
- አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ
- ወይዘሮ አዳነች አቤቤ
- ኢንጂነር ታከለ ኡማ
- አቶ ሽመልስ አብዲሳ
- አቶ ኡመር ሁሴን
- ወይዘሮ ጠይባ ሀሰን
- አቶ አዲሱ አረጋ
- ዶክተር ግርማ አመንቴ
- ዶክተር ቢቂላ ሁሪሳ
- ዶክተር ሚልኬሳ ሚደጋ
- ዶክተር ተሾመ አዱኛ
- አቶ ታዬ ደንደአ
- ዶክተር አለሙ ስሜ
- ዶክተር ቶላ በሪሶ
- አቶ ደመላሽ ገብረሚካኤል
- አቶ ግርማ ሀይሉ
- አቶ ወርቁ ጋቸና
- አቶ ሻፊ ሁሴን
- አቶ ቶሎሳ ገደፋ
- አቶ ፍቃዱ ተሰማ
- አቶ ብርሃኑ በቀለ
- አቶ አወሉ አብዲ
- አቶ ጌቱ ወዬሳ
- አቶ ካሳሁን ጎፌ
- አቶ መላኩ ፈንታ
- አቶ ታረቀኝ ገለታ
- አቶ አበራ ወርቁ
- አቶ መኩዬ መሃመድ
- አቶ አህመድ ቱሳ
- አቶ አሰግድ ጌታቸው
- አቶ ደንጌ ብሩ
- አቶ ነመራ ቡሊ
- አቶ አብዱልአዚዝ መሃመድ
- አቶ ሮባ ቱርጬ
- አቶ ጀማል ከድር
- አቶ መሃመድ ከማል
- አቶ መስፍን አሰፋ
- ወይዘሪት ሌሊሴ ለሚ
- አቶ ናስር ሁሴን
- አቶ ሞገስ ኢደኤ
- ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በመሆን ተመርጠዋል።