በአፋር ክልል በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ከ6 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ከነተጠርጣሪው መያዙን ፖሊስ ገለጸ - ኢዜአ አማርኛ
በአፋር ክልል በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ከ6 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ከነተጠርጣሪው መያዙን ፖሊስ ገለጸ
147
ነሐሴ 07 ቀን 2014 (ኢዜአ) በአፋር ክልል በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ ከ6 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ ከነተጠርጣሪው መያዙን የሰመራ ሎጊያ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።
የመምሪያዉ ዋና አዛዥ ኮማንደር ቢልኢ አህመድ እንደገለጹት፤ ገንዘቡ በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር ነሃሴ 05 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰአት ተኩል በከተማዉ ልዩ ስሙ ደረቅ ወደብ በሚባል ቦታ ሊያዝ ችሏል።
ከህብረተሰቡ ለፖሊስ በደረሰ ጥቆማ መሠረት በተደረገ ክትትል የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 2-B34960 አ/አ በሆነ ተሽከርካሪ ተደብቆ 6 ሚሊዮን 738 ሺህ ብር በላይ በህገወጥ መንገድ ሲጓጓዝ መያዙን ተናግረዋል።
ይህንን ገንዘብ በህገወጥ መንገድ ሲያዘዋውር የነበረው አሽከርካሪ ከነ መኪናው በቁጥጥር ስር ውሎ ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገበት እንደሆነም ጠቁመዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ፤