በክልሉ በ2015 በጀት ዓመት 2ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሠብሰብ ታቅዷል - ኢዜአ አማርኛ
በክልሉ በ2015 በጀት ዓመት 2ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ገቢ ለመሠብሰብ ታቅዷል
68
አሶሳ ነሐሴ 06 / 2014 ዓ.ም /ኢዜአ / በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በ2015 በጀት ዓመት 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ አስታወቁ::
የክልሉ ገቢዎች ባለስልጣን ለግብር ከፋዮች እና ባለድርሻ አካላት ያዘጋጀው የእውቅና መርሃ ግብር ዛሬ በአሶሳ እየተካሄደ ይገኛል::
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ በበጀት ዓመቱ ተፈናቃዮችን መልሶ ማቋቋምን ጨምሮ የህብረተሰቡን ጥያቄ ለመመለስ ልዩ ትኩረት ይሰጠዋል::
በክልሉ በ2015 በጀት ዓመት 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዷል ብለዋል::
በየደረጃው የሚገኙ መንግስታዊ ተቋማት ከሚያደርጉት ጥረት በተጨማሪ በተለይ የንግዱ ማህበረሰብ ግብር የመክፈል ሃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበዋል::
"ግብር እከፍላለሁ አስከፍላለሁ ህልውናዬን አረጋግጣለሁ" የመርሃ ግብሩ መሪቃል ነው::
መርሃ ግብሩ እስከ ነሐሴ 07 / 2014 ዓ.ም. ይቀጥላል::