የዱግዳና ቦራ ወረዳ ክላስተር የስንዴ ልማት በኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት እየተጎበኘ ነው - ኢዜአ አማርኛ
የዱግዳና ቦራ ወረዳ ክላስተር የስንዴ ልማት በኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት እየተጎበኘ ነው
133
ዱግዳ ነሀሴ 01/2014 /ኢዜአ /የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ በምስራቅ ሸዋ ዞን ዱግዳና ቦራ ወረዳ በክላስተር እየለማ ያለውን የስንዴ ማሳ እየጎበኙ ነው።
ፕሬዚዳንቱ የስንዴ ክላስተር ጉብኝታቸውን ቦራ ወረዳ ባርታ ሳሚ ቀበሌ ጀምረዋል ።
በዞኑ ከ280 ሺህ ሄክታር በላይ በተለያዩ ሰብሎች በኩታ ገጠም እየለማ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 188 ሺህ ሄክታሩ በስንዴ ክላስተር መልማቱ ተገልጿል ።
በኦሮሚያ ክልል በእስከ አሁኑ ሂደት ከ1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በኩታ ገጠም በስንዴ ዘር ተሸፍኗል ።