ከ24 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የውጭ አገራት ገንዘብና 6 ሺህ 84 ነጥብ 82 ግራም ወርቅ ተያዘ - ኢዜአ አማርኛ
ከ24 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የውጭ አገራት ገንዘብና 6 ሺህ 84 ነጥብ 82 ግራም ወርቅ ተያዘ
249
ሐምሌ 14 ቀን 2014 (ኢዜአ) 24 ሚሊዮን 339 ሺህ 280 ብር ግምት ያለው የውጭ አገራት ገንዘብ እና 6 ሺህ 84 ነጥብ 82 ግራም ወርቅ ተያዘ።
መነሻዉን አዲስ አበባ አድርጎ መድረሻዉን ሐረር ከተማ ለማድረግ አስቦ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 2አአ B33202 መኪና ቀረሳ ኬላ ሲደርስ በቀን 13/11/14 ዓ፡ም ከቀኑ 6:00 ሲል ሐረር ከተማ ሲደርስ ከሐረር ከተማ ፖሊስ ጋር በመሆን የአሜሪካና የካናዳ ዶላር፣ የእንግሊዝ ፓውንድ፣ የሳዑዲ ሪያል እና 6 ሺህ 84 ነጥብ 82 ግራም ወርቅ ከነ አዘዋዋሪዎቹ ተይዟል።
የተያዘው የውጭ አገሮች ገንዘብ 182 ሺህ 675 የአሜሪካ ዶላር፣ 5 ሺህ 530 የካናዳ ዶላር፣ 1 ሺህ 800 ፓዉንድ 67 ሺህ 145 የሳኡዲ ሪያል ከ ሁለት አዘዋዋሪዎች ጭምር በቁጥጥር ስር እንዲዉል ተደርጓል፡፡
በህገወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የተያዘው ገንዘብና ወርቅ ወደ ኢትዮጰያ ብር ሲቀየር 24 ሚሊዮን 339 ሺህ 280 ብር እንደሚሆን ምንጮቻችን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ፤