የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት ያስገነባው የረገ ኤያት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመረቀ

184

ሰኔ 04 ቀን 2014 (ኢዜአ) የቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ያስገነባው የረገ ኤያት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመረቀ።

በምርቃት ስነ-ስርዓቱ ላይ ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ ዝናሽ ታያቸው፣ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ርስቱ ይርዳ ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መሀመድ ጀማል እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአካባቢው ሽማግሌዎችና የሐይማኖት አባቶች ተገኝተዋል።

May be an image of 8 people, people standing and outdoors

ትምህርት ቤቱ በውስጡ 10 መማሪያ ክፍሎች ፣ ቤተ -ሙከራ፣ ቤተ-መጻሕፍት፣ የተማሪ ክሊኒክ ፣የአስተዳደር ሕንጻና የስብሰባ አዳራሽ ያካተተ ነው ።

በወረዳው ማመዴ ቀበሌ የተገነባው ይህ ትምህርት ቤት በክልሉ በቀዳማዊት እመቤት ጽህፈት ቤት ተገንብቶ ለምረቃ የበቃ ሁለተኛው ትምህርት ቤት መሆኑ ተመላክቷል ።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም