ዩኒቨርስቲው አዲስ ገቢ ተማሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል - ኢዜአ አማርኛ
ዩኒቨርስቲው አዲስ ገቢ ተማሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል
112
ሆሳዕና:ግንቦት 15/2014 (ኢዜአ) የወራቤ ዩኒቨርስቲ ከ3 ሺህ 200 በላይ አዲስ ገቢ ተማሪዎችን ዛሬ እየተቀበለ ነው ።
የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች ከመናኸሪያ ጀምሮ የትራንስፖርት አማራጭ በማቅረብ ጭምር አቀባበል እንዳደረገላቸው ተገልጿል።
በዩኒቨርሲቲው ነባር ተማሪዎችና ከወራቤ ከተማ የተውጣጡ ወጣቶች በመቀናጀት ነው ለተማሪዎቹ አቀባበል እያደረጉ የሚገኙት ።
በቅበላ መርሐ ግብሩ ላይ የዩኒቨርሲቲውና የዞኑ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችን ጨምሮ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የአካባቢው ነዋሪ ማህበረሰብ ተገኝተዋል።