በሀዋሳ “ ለአረጋዊያን ክብር እንጓዛለን ” በሚል መሪ ሀሳብ የእግር ጉዞ እየተካሄደ ነው - ኢዜአ አማርኛ
በሀዋሳ “ ለአረጋዊያን ክብር እንጓዛለን ” በሚል መሪ ሀሳብ የእግር ጉዞ እየተካሄደ ነው
134
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 14 ቀን 2014 (ኢዜአ) በሀዋሳ “ለአረጋዊያን ክብር እንጓዛለን” በሚል መሪ ሀሳብ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተሳተፉበት የእግር ጉዞ በመካሄድ ላይ ነው ።
በመርሀ-ግብሩ ላይ የሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ መስራችና ዋና ስራ አስኬያጅ ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ፣ታዋቂ አርቲስቶች፣ የመገናኛ ብዙሀን ባለሙያዎች፣ የመንግስት የሥራ ኃፊዎች፣ እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ።
የእግር ጉዞው ዋና ዓላማው ትናንት ታሪክ የሰሩ አሁን ግን በብዙ ችግር ውስጥ የሚገኙ አቅመ ደካማ አረጋዊያንን በተቻለ ሁሉ የመደገፍ ባህልን ማዳበርና ተሳትፎ መጨመር ነው ተብሏል።
በሁሉም እድሜ ክልል ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች በዚህ የእግር ጉዞ እየተሳተፉ ይገኛሉ።