ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች የተካፈሉበት የአፍጥር ስነ-ስርዓት በጅማ ተካሄደ - ኢዜአ አማርኛ
ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች የተካፈሉበት የአፍጥር ስነ-ስርዓት በጅማ ተካሄደ
96
ጅማ፣መጋቢት 26 ቀን 2014 (ኢዜአ) ሚኒስትሮችና ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች የተካፈሉበት የረመዳን የአፍጥር ስነ-ስርዓት በጅማ ከተማ ተካሄዷል።
የአፍጥር ስነ-ስርዓቱ "ለሀገራችን አንድነትና ፍቅር" በሚል መሪ ሀሳብ ነው የተካሄደው።
የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ወይዘሮ ናሲሴ ጫሊ፣የመንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ በአፍጥር ስነ-ስርዓቱ ላይ ተካፍለዋል።
ሚኒስትሮቹና የስራ ሀላፊዎቹ ዛሬ በጅማ ከተማ ጀሬን መናገሻ ላይ የሚገኘውን የንጉሥ አባጅፋርን ቤተ መንግስት የእድሳት ሂደትን የደረሰበትን ሁኔታ ይጎበኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።