ጤና ሚኒስትሯ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት ኢሌኒ መሀመድ መታሰቢያ ሆስፒታል የሲቲ ስካን ማሽን ስራ አስጀመሩ - ኢዜአ አማርኛ
ጤና ሚኒስትሯ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት ኢሌኒ መሀመድ መታሰቢያ ሆስፒታል የሲቲ ስካን ማሽን ስራ አስጀመሩ
102
ሆሳዕና የካቲት 27/2014 (ኢዜአ) የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በዋቸሞ ዩንቨርስቲ የንግስት ኢሌኒ መሀመድ መታሰቢያ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከ45 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ተደርጎበት የተተከለ የሲቲ ስካን ማሽን መርቀው ስራ አስጀመሩ ።
ሚኒስትሯ በሆስፒታሉ ከ2 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ ወጭ ለሚገነባው የኦክስጅን ማምረቻና የእናቶችና ህፃናት ጤና አገልግሎት መስጫ ማእከል የመሰረተ ድንጋይ አስቀምጠዋል ።
የንግስት ኢሌኒ መሀመድ መታሰቢያ ኮምፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በ1973 ዓ.ም ግንባታው ተጠናቆ የህክምና አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ይታወሳል ።
በስነ ስርአቱ ላይ የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ እንዳሻው ሽብሩን ጨምሮ ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።