በአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ የተመራ ልኡክ ጅግጅጋ ከተማ ገባ - ኢዜአ አማርኛ
በአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ የተመራ ልኡክ ጅግጅጋ ከተማ ገባ
112
አዲስ አበባ ጥር 25/2014(ኢዜአ) በአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ የተመራ ልኡክ በሶማሌ ክልል በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ ጅግጅጋ ከተማ ገባ።
የልኡክ ቡድኑ ጅግጅጋ ገራድ ዊልዋል አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ አቀባበል አድርገዋል።
ልኡኩ ወደ ስፍራው ያቀናው በክልሉ በተከሰተው ድርቅ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ መሆኑ ታውቋል።
የአማራ ክልል፤ በኦሮሚያ ክልል ጎጂና ቦረና አካባቢዎች በድርቅ ለደረሰው ጉዳት በትናንትናው እለት የእንስሳት መኖ ድጋፍ ማድረጉ ይታወቃል።