የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለ 36 ወለል የዋና መስሪያ ቤት ሕንፃ ሊያስገነባ ነው

81

ጥር 14 ቀን 2014 (ኢዜአ) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለ 36 ወለል የዋና መስሪያ ቤት ሕንፃ ሊያስገነባ መሆኑ ተገለጸ።

ግንባታው የኤሌክትሪክ አገልግሎት ደንበኞች መስፋትን ተከትሎ በቴክኖሎጂ የተደገፈና ተወዳዳሪ አገልግሎት መስጠትን ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ተመልክቷል።

ለሚገነባው ሕንጻ የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥና የግንባታ ማስጀመር መርሃ ግብር እየተከናወነ ነው።

የሕንጻው ግንባታ በአራት ዓመት እንደሚጠናቀቅ ተነግሯል።

ኢትዮጵያን እናልማ፣እንገንባ፣እንዘጋጅ

‼️

ሀገርን በዘላቂነት እናልማ

‼️

የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ

‼️

ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ

‼️
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም