የሲዳማ ክልል ምክር ቤት አንደኛ መደበኛ ጉባኤ ነገ ይጀመራል - ኢዜአ አማርኛ
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት አንደኛ መደበኛ ጉባኤ ነገ ይጀመራል
71
ሀዋሳ ታህሳስ 21/2014 (ኢዜአ) የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ ዙር አንደኛ የሥራ ዘመን አንደኛ መደበኛ ጉባኤ ነገ እንደሚጀምር ተገለጸ።
የምክር ቤቱ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ አዲሱ ዶራሞ ለኢዜአ እንደገለጹት ፤ ጉባኤው በሚኖረው የሁለት ቀናት ቆይታ የምክር ቤቱን ስድስተኛ ዙር መስራች ጉባኤ ቃለ ጉባኤ እንደሚያፀደቅ ይጠበቃል።
እንዲሁም የክልሉን መንግስት የአስር ዓመት መሪ ዕቅድ ፣ የህግ አውጪ፣ህግ አስፈጻሚና ህግ ተርጓሚ የመንግስት አካላት የ2014 በጀት ዕቅድ ፣ የምክር ቤት የአባላት ሥነ-ምግባር ደንብ ላይ ምከር ቤቱ ከሚወያይባቸው አጀንዳዎች መካከል ጠቅሰዋል።
ጉባዔው የተለያዩ ሹመቶችን ተቀብሎ እንደሚያፀድቅ የሚጠበቅ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጨምረው ገልጸዋል።