የዳያስፖራዎች የአቀባባል ስነ ስርዓት በወዳጅነት አደባባይ እየተካሄደ ነው - ኢዜአ አማርኛ
የዳያስፖራዎች የአቀባባል ስነ ስርዓት በወዳጅነት አደባባይ እየተካሄደ ነው
84
ታህሳስ 20 ቀን 2014 (ኢዜአ) የጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ “የአንድ ሚሊዮን ዳያስፖራ የአገር ቤት ጉዞ ጥሪ” ተቀብለው ለመጡ ዳያስፖራዎች የአቀባባል ስነ ስርዓት በወዳጅነት አደባባይ እየተካሄደ ነው።
በስነ ስርዓቱ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤና ሌሎች የመንግስት የስራ ሃላፊዎች፣ የዳያስፖራ ማህበረሰብ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
የመርሃ ግብሩ ታዳሚዎች በወዳጅነት አደባባይ ለዳያስፖራዎቹ የአገር ቤት ጥሪ የተዘጋጀውን አውደ ርዕይ ጎብኝተዋል።
በውጭ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወደ አገር ቤት እንዲመጡ የቀረበላቸውን ጥሪ ተቀብለው በርካታ ዳያስፖራዎች ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ መሆኑ ይታወቃል።