አካዳሚው ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ15 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የአይነት ድጋፍ አደረገ - ኢዜአ አማርኛ
አካዳሚው ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ15 ሚሊየን ብር በላይ የገንዘብና የአይነት ድጋፍ አደረገ
70
አዲስ አበባ፣ ህዳር 21/2014(ኢዜአ) የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ለተፈናቀሉ ወገኖች 15 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የገንዘብና የአይነት ድጋፍ አደረገ።
ድጋፉን የአካዳሚው ፕሬዝዳንት ዶክተር ምህረት ደበበ፤ ለአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ምትኩ ካሳ በዛሬው እለት አስረክበዋል።
ከአጠቃላይ ድጋፉ የአካዳሚው ሰራተኞች የወር ደሞዛቸውን በመለገስ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር ሲያበረክቱ ቀሪውን አካዳሚው መለገሱ ታውቋል።