ለዩጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቨኒ አሸኛኘት ተደረገላቸው - ኢዜአ አማርኛ
ለዩጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቨኒ አሸኛኘት ተደረገላቸው
67
መስከረም 25/2014 (ኢዜአ) በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በዓለ ሲመት ላይ የታደሙት የዩጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቨኒ ወደ አገራቸው አቅንተዋል።
በወቅቱም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በመገኘት ለፕሬዝዳንቱ አሸኛኘት አድርገውላቸዋል።
በአሸኛኘት ስነ-ስርዓቱ ላይ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ እና ሌሎችም ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል።