ኢትዮ ቴሌ ኮም የአራተኛ ትውልድ አገልግሎት በደቡብ ሪጅን የማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት እያካሄደ ነው - ኢዜአ አማርኛ
ኢትዮ ቴሌ ኮም የአራተኛ ትውልድ አገልግሎት በደቡብ ሪጅን የማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት እያካሄደ ነው
132
ሀዋሳ፤ ሰኔ 29/2013 (ኢዜአ )ኢትዮ ቴሌ ኮም የአራተኛ ትውልድ / 4ጂ/ ኢንተርኔት አድቫንስድ አገልግሎት በደቡብ ሪጅን የማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት በሀዋሳ ከተማ እያካሄደ ነው።
አገልግሎቱ በሀዋሳ፣ ሻሸመኔ፣ አርሲ ነገሌና ዲላን ጨምሮ በሪጅኑ 12 ከተሞችን እንደሚሸፍን በስነ-ስርዓቱ ላይ ተገልጿል።
በዚሀም አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ደንበኞች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተመልክቷል።
በስነ-ስርዓቱ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ፣ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ረዳት ፕሮፌሰር ፀጋዬ ቱኬና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።