በአዳማ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው - ኢዜአ አማርኛ
በአዳማ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሔደ ነው
90
አዳማ የካቲት 15/ 2012 (ኢዜአ) የአዳማ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ለውጡን በመደገፍ የድጋፍ ሰልፍ እያካሄዱ ነው:: የአዳማ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ለውጡን በመደገፍ ዛሬ ከጧቱ 12 ሰዓት ጀምረው ደማቅ የድጋፍ ሰልፍ በማካሔድ ላይ ናቸው ። ሰልፈኞቹ በትግላችን ያመጣነውን ለውጥ እንጠብቃለን እንከባከባለን ! ለለውጡ ውጤታማነት የድርሻችንን እንወጣለን ! የሚል መፈክር አንግበው ወደ አዳማ መስቀል አደባባይ በማምራት ላይ ናቸው ። መነሻችን መደመር መድረሻችን ደግሞ ብልፅግና ነው ! ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን በመጠበቅ ለውጡን ከዳር እናደርሳለን ! የሚሉ መፈክሮችም ሰልፈኞቹ ከሚያስተጋቡዋቸው መካከል የሚጠቀሱ ናቸው ። የሰልፉ ተሳታፊ ህዝብ ቁጥር ከ70 ሺህ በላይ መሆኑን በቦታው የሚገኙ የኢዜአ ሪፖርተሮች የዘገቡ ሲሆን በአዳማው መስቀል አደባባይ የኦሮሚያ ክልል ፣ የምስራቅ ሸዋ ዞንና የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል ።