በጀኔራል ኻሊፋ ሃፍታር የሚመራው ጦር የትሪፖሊ ከተማ ን በቁጥጥር ስር ለማዋል ጦሩንእንደሚያዘምት አስታወቀ - ኢዜአ አማርኛ
በጀኔራል ኻሊፋ ሃፍታር የሚመራው ጦር የትሪፖሊ ከተማ ን በቁጥጥር ስር ለማዋል ጦሩንእንደሚያዘምት አስታወቀ
86
ኢዜአ፤ ታህሳስ 3/2012 በተባባሩት መንግስታት ድርጅት ድጋፍ የሚደረግለት የሊቢያ መንግስት መቀመጫ የሆነችውን ትሪፖሊ በቁጥጥር ስር ለማዋል ጀኔራል ኻሊፋ ሃፍታር ትዕዛዝ ማስተላለፈቸው ተገልጸዋል፡፡
በተባበሩት መንግስታት የሚደገፈውን መንግስት ጠራርጎ በማስወጣት ዋና ከተማዋ ትሪፖሊን ለመቆጣጠር ምንም ዓይነት የምናባክነው ግዜ የለንም ብሏል ጀነራል ካሊፋ ሃፍታር ፡፡
ጀኔራል ኻሊፋ ሃፍታር የሊቢያ ዋና ከተማ ትሪፖሊን ነጻ ለማውጣት የሚስችላቸውን ወሳኝ ውግያ ለማድረግ ቅድመ ዝግጅት ማጠናቃቀቸውን ገልፀዋል፡፡
ጀኔራል ኻሊፋ ሃፍታር ይህን ቢሉም በጀነራል ካሊፋ ሃፍታር ወታደሮች በኩል ተቃውሞ ሳይገጥሟቸው እንዳልቀረ ተገልጸዋል፡፡
እስከ አሁን በአካባቢው ምንም ዓይነት ወታደራዊ እንቅስቃሴ መኖሩን የሚያሳይ መረጃ አልተገኘም ሲል የዘገበው አልጀዚራ ነው።