በትግራይ ደቡባዊ ዞን መኾኒ ከተማ የደረሰው የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት አደረሰ - ኢዜአ አማርኛ
በትግራይ ደቡባዊ ዞን መኾኒ ከተማ የደረሰው የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት አደረሰ
106
ኢዜአ ህዳር 26 ቀን 2012 ዓም በትግራይ ደቡባዊ ዞን መኾኒ ከተማ ትናንት ሌሊት በደረሰው የእሳት አደጋ 2 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን የራያ አዘቦ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ገለፀ ። የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ሓየሎም ረዳኢ ለኢዜአ እንደገለፁት የእሳት አደጋው ያጋጠመው ትናንት ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይ ነው የደረሰው ። የአደጋው መንስኤ የኤሌክትሪክ ገመድ እርስ በራሱ ተጠላልፎ በፈጠረው እሳት ሲሆን በከተማው የገበያ ቦታ ሁለት ሚሊዮን ብር የሚገመት ጉዳት አድርሷል ። በአደጋው የ56 ነጋዴዎች ዘይትና ጫማ ሙሉ በሙሉ ወድሟል ። ህብረተሰቡ ባደረገው ርብርብ በሌሎች መኖሪያ ቤቶችና የንግድ ሱቆች ላይ ተጨማሪ አደጋ ሳያደርስ በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል ።