የአዲሱ ውህድ ፓርቲ ህገ ደንብ ጸደቀ - ኢዜአ አማርኛ
የአዲሱ ውህድ ፓርቲ ህገ ደንብ ጸደቀ
116
ኢዜአ፤ ህዳር 12/2012 የኢህአዴግ ምክር ቤት የአዲሱን ውህድ ፓርቲ ህገ ደንብ በሙሉ ድምጽ አጸደቀ፡፡
የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲ ግንባር /ኢህአዴግ/ ምክር ቤት ለሀሉት ቀናት ሲያካሄድ የነበረውን ስብሰባ አጠናቋል፡፡
በሁለተኛ ቀን ውሎው ዛሬ የአዲሱ ውህድ ፓርቲ ህገ ደንብ ላይ በጥልቀት ከመከረ በኋላ የተገኙት አባላት በሙሉ ድምጽ ማጽደቃቸውን ከኢህአዴግ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
በመጀመሪያ ቀን ውሎውም ምክር ቤቱ የፓርቲውን ውህደትና ፓርቲው ወደ ፊት የሚመራበት ፕሮግራም ላይ በመምከር አጽድቋል፡፡