የቡኖ በደሌ ዞን ነዋሪዎች የመሰረተ ልማት ችግር እንዲፈታላቸው ጠየቁ

63

መቱ፤ ኢዜአ፤ ጥቅምት 10 ቀን 2012 ዓም  በኦሮሚያ ክልል የቡኖ በደሌ ዞን ነዋሪዎች በአካባቢያቸውን የሚታየውን የመሰረተ ልማት ችግር እንዲፈታላቸው ጠየቁ ።

የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ መንግስት የምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢዎች በልማት በኩል ያሉባቸውን ችግሮች በመገንዘብ ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ጥረት እያደረገ መሆኑን አስረድተዋል ::

የቡኖ በደሌ ወረዳ ነዋሪዎች የልማት ጥያቄአቸውን ያቀረቡት ትናንት ከክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ጋር በተወያዩበት ወቅት ነው ።

ከዞኑ የተለያዩ ወረዳዎች የተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች የክልሉ መንግስት ያሉባቸውን የልማት ችግሮች    እንዲፈታላቸው ጠይቀዋል::

በውይይቱ ከተነሱ ጥያቄዎች መካከል መንግስት በየጊዜው የሚቆራረጠው የመብራት አገልግሎት በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ በመሆኑ በአፋጣኝ ሊፈታልን ይገባል ብለዋል ።

የበደሌ ሆስፒታል ለአካባቢው ማህበረሰብ የተሟላ የህክምና አገልግሎት እንዲሰጥ ወደ ሪፈራል ሆስፒታል እንዲያድግላቸውም ነዋሪዎቹ ጠይቀዋል ።

የመቱ ዩኒቨርስቲ የበደሌ ግብርናና ደን ሳይንስ ኮሌጅ ወደ ሙሉ ዩኒቨርስቲነት  እንዲያድግላቸውም ነዋሪዎቹ ለምክትል ፕሬዚዳንቱ አንስተውላቸዋል ::

በአካባቢው ለቡና ፣ አትክልትና ፍራፍሬና ለማር ምርት ያለውን አመቺነት በመጠቀም አርሶአደሩ ምርቱን ለውጭ ገበያ በማቅረብ ተጠቃሚ እንዲሆን መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍና እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል::

ወደ ዴዴሳ ወረዳ በሰፈራ መልክ የመጡና በቂ መሬት ያላገኙትን አባወሯዎች ችግር ለመፍታትም የክልሉ መንግስት እየሰራ በመሆኑ በአጭር ጊዜ ውስጥ ችግሩ እንደሚቀረፍ አስረድተዋል::

መንግስት የልማት ችግሮችን ለመፍታት ለሚያደርገው ጥረት የህብረተሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ ተሳትፎውን አጠናክሮ እንዲቀጥልም ምክትል ፕሬዚዳንቱ አስገንዝበዋል ::

     
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም