ናይጄሪያ በአፍሮ አፍሪካ የቅርጫት ኳስ ሻምፒዮና አሸናፊ ሆነች

66
ነሀሴ 13/2011 በአፍሪካ የሴቶች ቅርጫት ኳስ ሻምፒዮና ናይጄሪያ ሴኔጋልን በማሸነፍ የአፍሪካ ቅርጫት ኳስ ሻምፒዮን ለመሆን በቅታለች፡፡ ናይጄሪያ ሻምፒዮን ለመሆን የበቃችው ሴኔጋልን በአምስት የነጥብ ልዩነት 60 ለ55 በሆነ ውጤት በመርታት ነው፡፡ የናይጄሪያው ፕሬዘዳንት ሙሀመድ መቡሃሪ የናይጄሪ ሴቶች ቅርጫት ኳስ ቡድን ባስመዘገበው ድል መደሰታቸውንና ለቡድኑና ለመላው ህዝባቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት በቲውተር ገጻቸው ማሰራጨታቸውን ነው አልጀዚራ በድረገፁ ያስነበበው፡፡
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም