ኢራፓ እና ኢዜማ ተዋሃዱ - ኢዜአ አማርኛ
ኢራፓ እና ኢዜማ ተዋሃዱ
122
አዲስ አበባ ኢዜአ ሀምሌ 8/2011 የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ /ኢራፓ/ እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለፍትህ ፓርቲ /ኢዜማ/ ተዋሃዱ። የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ ኢራፓ/ የሚለው መጠሪያው ከስሞ ከኢትዮጵያ ዜጎች ለፍትህ ፓርቲ ጋር ውህደት መፍጠሩን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ኢዜማ ግንቦት 2 ቀን 2011 ዓ.ም በይፋ ሲቋቋም ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋን በድርጅት መሪነት፣ አቶ አንዷለም አራጌን በምክትልነት፣ እንዲሁም አቶ የሺዋስ አሰፋን የፓርቲው ሊቀመንበር ፣ ዶክተር ጫኔ ከበደን ደግሞ ምክትል ሊቀመንበር አድረጎ መሰየሙ ይታወሳል። ፓርቲው ያልተማከለ አስተዳደር (ፌዴራላዊ) ሥርዓትን መከተለን ምርጫው ያደረገ ሲሆን ከፍተኛው የመንግሥት ሃላፊነት በሕዝብ ቀጥታ ምርጫ በሚመረጥ ፕሬዝዳንታዊ ሥርዓት ይከተላል።