በአፍሪካ ዋንጫ ሴኔጋልና ናይጀሪያ ወደ ግማሽ ፍፃሜ አለፉ - ኢዜአ አማርኛ
በአፍሪካ ዋንጫ ሴኔጋልና ናይጀሪያ ወደ ግማሽ ፍፃሜ አለፉ
78
ኢዜአ ሀምሌ 4/2011በግብፅ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2019 የአፍርካ ዋንጫ ትናንት ምሽት ሁለት የሩብ ፍፃሜ ጨዋታዎች ተደርገዋል።
ናይጀሪያ ደቡብ አፍሪካን በገጠመችበት ጨዋታ በሳሙኤል ቹኩዌዜ እና ትሩስት ኤኮንግ ግቦች 2 ለ 1 ስታሸንፍ ሴኔጋል ቤኒንን በኢድሪሳ ጉዬ ግብ 1 ለ 0 ረትታለች።
የደቡብ አፍሪካን ከሽንፈት ያላዳነች ግብ ቦንጋኒ ዙንጉ ከመረብ አዋህዷል።
ይህን ተከትሎም ናይጀሪያና ሴኔጋል ወደ ግማሽ ፍፃሜው አልፈዋል።
ምንጭ፡-ቢቢሲ